1ይ ቆሮንቶስ 2:1-2 - :ኣሕዋተየ፡ ኣነ ድማ ኣብ ማእከልኩም ከሎኹ፡ ብዘይ የሱስ ክርስቶስ፡ ንሱ ኸኣ እቲ እተሰቕለ፡ ሓደ ነገር እኳ ኸም ዘይ

በ ስም ኣብ ወወልድ ወ መንፈስ ቅዱስ ኣሃዱ ኣምላክ ኣሜን።

Friday 11 May 2012

ሰበር ዜና መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝና አባ ሠረቀ ብርሃን ወ/ሳሙኤል ከተከከሰሱበት የኑፋቄ ክስ ነፃ ወጡ!!


ሰበር ዜና መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝና አባ ሠረቀ ብርሃን ወ/ሳሙኤል ከተከከሰሱበት የኑፋቄ ክስ ነፃ ወጡ!!


ውሳኔው በማኅበረ ቅዱሳን ላይ መንፈሳዊና ሞራላዊ ክስረት የሚያደርስ ሲሆን በዓለም ዙሪያ ላሉ የቤተክርስቲያናችን ቤተሰቦች ታላቅ ብሥራት ነው
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ ትላንት ሐሙስ ግንቦት 2 ቀን 2004 ዓ.ም ቀጥሎ በዋለው ስብሰባ መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝንና አባ ሠረቀ ወ/ሳሙኤልን ከተከሰሱበት "የፕሮቴስታንታዊ ተሀድሶ ኑፋቄ" ክስ ነፃ ያወጣቸው መሆኑን የደረሰን መረጃ አመለከተ፡፡
"ማኅበረ ቅዱሳን" በተለይ በሁለቱ የቤተክርስቲያን ልጆች ላይ ያስነሳው ሁከትና የክስ ድሪቶ በሥጋዊ ዓይን ሲታይ እጅግ በጣም ታላቅ ነበር፡፡ መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ከተሰጠው የስብከት ፀጋ በተጨማሪ ማቆች አደብ እንዲገዙ በሚሰጣቸው ምክር በመበሳጨት እንዲሁም አባሠረቀ ብርሃን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ በነበሩበት ወቅት ሕግና ሥርዓትን ጠብቆ እንዲይዝ፣ እዚህም እዚያም እየዘለለ እንዳያውክና መዋቅሩን ጠብቆ እንዲሠራ፣ እንዲሁም ስሕተቶቹን እንዲያርም አግባብ ባለው መንገድ ስለያዙት በሁለቱ አገልጋዮች ላይ ያወረደው ውርጅብኝ በምዕመናን ዘንድ አካላዊና ሥነ ልቦናዊ እንዲሁም መንፈሳዊ ጫናን ያሳደረ ነበር፡፡
በመጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝና እና በአባ ሠረቀ ብርሃን ወ/ሳሙኤል ላይ የቀረበው የሐሰት ክስ ድሪቶ ሊገፈፍ የቻለው በአገልግሎት ዘመኖቻቸው የፈጸሟቸው የጽሑፍ፣ የምስልና የድምፅ አስተምህሮቻቸው ተፈትሾ ሕጸጽ ባለመገኘቱ መሆኑ ታውቋል፡፡ ይህ በሊቃውንት ጉባዔ የተመረመረው የአስተምህሮዎቻቸው ውጤት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ ከመረመረውና ከተወያየበት በኋላ ያለ ምንም ልዩነት በሙሉ ድምፅ አጽድቆታል፡፡
ወትሮም ቢሆን "ማኅበረ ቅዱሳን" ከንቱ ጩኸትና ልፍለፋ ካልሆነ በስተቀር አንዳች ተጨባጭ እውነት ያዘለ ቁም ነገር እንደሌለው ይታወቃል፡፡ ቤተክርስቲያን የሰዎች ስብስብ እንደመሆኗ መጠን ከሰዎች የአገልግሎት ስሕተት ነፃ ናት ልትባል አትችልም፡፡ ሆኖም እነዚህ ስሕተቶች ትልቅም ይሁኑ ትንሽ የሚታረሙበት አግባብ አላቸው፡፡ በተለይም በቀኖና ቤተክርስቲያንና በፍትሐ ነገሥቱ አገልጋዮችና ምዕመናን እንደየደረጃቸው ስሕተት ሲፈጽሙ የሚታረሙበትና ከእናት ቤተክርስቲያን ጋር ታርቀው ስለሚሄዱበት ሁኔታ በግልጽ ተቀምጧል፡፡ ነገር ግን ማኅበረ ቅዱሳን ራሱን ከቀኖና ቤተክርስቲያን፣ ከፍትሐ ነገሥት፣ ከጠቅላይ ቤተክህነት፣ ከሊቃውንት ጉባዔና ከሲኖዶስ በላይ በማስቀመጥ፣ ከሳሽና ፈራጅ በመሆን በቤተክርስቲያን ላይ ከፍተኛ ቀውስ አስከትሏል፡፡
ለዓመታት በዘለቀው በዚህ ቀውስ የተዘጉ ቤተመቅደሶች፣ የተሰደዱ ምዕመናንና አገልጋዮች፣ የደረሰ ድብደባ፣ እንግልት፣ እሥራትና ሞት፣ በዚህ ሁኔታ ድንግርግር ውስጥ ገብተው የዕምነት እሴታቸው የተሸረሸረባቸው ስንቶች እንደሆኑ ቤቱ ይቁጠረው፡፡ በተለይም የዋሃን ተከታዮቹ መሪዎቻቸው የደገሱትን ሳያውቁ በዘረጉት የሁከት ፕሮጀክት በደመነፍስ በመሳተፍ ስንቱን ወንድሞቻቸውንና እህቶቻቸውን እንደበደሉ እና የቤተክርስቲያንን የአምልኮ ሥርዓት እንዳወኩ ማስተዋል ይቻላል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን ደጋግመን እንደምንለው ፖለቲካዊ የማፊያ ድርጅት እንጂ ሃይማኖታዊ አይደለም፡፡ የአባላት ቁጥሩና ዝርዝር በቤተክርስቲያንና በመንግሥት አይታወቅም፤ የሀብትና የገንዘብ ምንጩ በትክክል አይታወቅም፣ የወጪውና የገቢው  አርዕስት አይመዘገብም፤ ሀብትና ንብረቱና የፋይናንስ እንቅስቃሴው ኦዲት ተደርጎ አይታወቅም፡፡ ኦዲት ለማሰደረግም ከቤተክርስቲያን አቅም በላይ ሆኗል፡፡
በዚህ የጨለማ ዓለም እንቅስቃሴው ሲዳክር በዝቋላ ገዳምና በዋልድባ ገዳም ሳቢያ ፖለቲካዊ ማንነቱ በይበልጥ የተጋለጠው "ማኅበረ ቅዱሳን" ኪሣራ ያጋጠመው ሲሆን አሁንም ባልተሰጠው ሥልጣን "የፕሮቴሰታንታዊ ተሀድሶ" አታሞውን ሲደልቅ የከረመበት የዓመታት ልፋቱ እንደጉም ተንኖበት መንፈሳዊ ኪሣራ ውስጥም ለመዘፈቅ ተገዷል፡፡
የመጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝና የአባ ሠረቀ ብርሃን ወ/ሳሙኤል ነፃነት በቅን አማንያን ዘንድ ቀድሞም የሚታወቅ ቢሆንም፣ በተለይ በተቀነባበረና በፈጠራ የሐሰት ክስ የተከመረባቸው የጎደፈ ስም እንደዚህ ጥርት ባለና በተረጋጋ ሁኔታ መወሰንና መንጻት መቻሉ አስደሳች ነው፡፡ መቶ በጎች ያሉት ሰው አንዲት በግ ብትጠፋበትና መልሶ ቢያገኛት ካልጠፉት ከዘጠና ዘጠኙ በጎች ይልቅ ጠፍታ በተገኘችው በግ ደስ እንደሚለው፣ የእነዚህ ሁለት አገልጋዮች እንደ ጠላት ሃሣብ ሳይሆን በበረቱ መቆየት ለሁላችንም ብሥራት ነው፡፡
እግዚአብሔር በምሕረቱና በቸርነቱ ይጠብቀን!!!
አሜን!!!

ማኅበረ ቅዱሳን አቡነ ጳውሎስን ከሥልጣን ለማውረድ ታጥቆ ተነስቷል

  • በጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰራተኞች ስም ደብዳቤም አሰራጭቷል
ሰሞኑን እየገጠመው ካለው ችግርና ፓትርያርኩም በውሳኔዎች ላይ ቆራጥ እየሆኑ በመምጣታቸው የእሳቸው ስልጣን ላይ መቆየት ለህልውናዬ ያሰጋኛል ብሎ በማሰቡ ማኅበረ ቅዱሳን እሳቸውንን የማውረድ ዘመቻ ውስጥ ውስጡን ጀምሯል፡፡ በተለይም በጠ/ቤተ ክህነቱ ሠራተኞች ስም “የዳኛ ያለህ! ለቤተ ክርስቲያኒቱ ዳኝነት ይታይላት” በሚል ርዕስ ያሰራጨው ጽሑፍ ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የደረሰ ሲሆን ይህንኑ እንደ ግብአት ተጠቅመው አጀንዳ ለማስያዝና ቅዱስነታቸውንን የማውረድ ሴራ እንዲሸርቡ የተመከሩ ጳጳሳት እንዳሉ ይነገራል፡፡

ምንም እንኳ የጽሁፉ ምንጭ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰራተኞች ናቸው ቢባልም ጹሁፉ ግን ከማኅበረ ቅዱሳን እንደወጣ እና አብዛኛው የጠ/ቤተ ክህነት ሠራተኞችችም ጽሁፉ መጻፉን እንኳን እንደማያውቁ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ከዚህ በጠ/ቤተ ክህነቱ ሠራተኞች ስም ካሰራጨው ጽሁፍ በተጨማሪ በቆዩትና አዳዲስ እየከፈታቸው ባሉ ብሎጎች ሀሳቡን እያንሸራሸረ የሚገኝ ሲሆን ይህም የታቀደው ተሳክቶ ፓትርያርኩ ቢነሱ ሕዝቡ ግር እንዳይለው ግንዛቤ መፍጠሪያ መንገድ መሆኑም ታውቋል፡፡

 በአንዳንድ ብሎጎችም ቅዱስነታቸውን “እናሸንፋቸውና // ሰላም ታግኝ” በማለት ይፋ የስልጣን ማፈናቀል ዘመቻ ከፍተዋል፡፡ ብሎጎቹ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰራተኞች ስም ከተጻፋ ደብዳቤ ጋር በይዘትም በቅርጽም ተመሳሳይ የሆነ ጽሁፍ የለቀቁ ሲሆን ልዩነቱ ብሎጎቹ ላይ ያለው ጽሁፍ በግል አስተያየት ስም የተጻፉ መሆናቸው ነው፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን ብሎጎች ጽሁፉን የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰራተኞች ጻፉት ከማለት አልፎ የት  ተሰባስበው እና ምን ተነጋግረው ለዚህ ውሳኔ እንደደረሱ ለማብራራት አልሞከሩም፡፡ ምክንያቱም ጽሁፉ መፃፉን በማያውቁ የቤተ ክህነት ሰራተኞች ስም የጻፈው ማቅ ነውና፡፡ በዚህ ደብዳቤና በሌሎች የቅስቀሳ መንገድም ብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት አሳስቶና አነሳስቶ የሲኖዶሱን ጉባኤ የረብሻ መድረክ ለማድረግና በግርግሩም ፓትርያርኩን ለማንሳት የታሰበና የታቀደበት ሲሆን በብዙዎች ዘንድ የማቅ የሞት ሽረት ትግል የሚታይበት የሲኖዶስ ስብሰባ ነው እየተባለ ነው፡፡
http://www.awdemihret.blogspot.com/2012/05/blog-post_3442.html 

ቅዱስ ሲኖዶስ አባ ሠረቀ ብርሃንና ዲ/ን በጋሻውንን የኃይማኖት ህጸጽ የለባቸውም ተሃድሶ መናፍቃንም አይደሉም አለ

ቅዱስ ሲኖዶስ አባ ሠረቀ ብርሃንና ዲ/ን በጋሻውንን የኃይማኖት ህጸጽ የለባቸውም ተሃድሶ መናፍቃንም አይደሉም አለ

 
በትናንትነው ዕለት የተጀመረው የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ የጀመረው ከጥቅምቱ ስብሰባ ወደ ግንቦት የተዘዋወሩ ጉዳዮችንን በመመልከት ሲሆን የመጀመሪያ አጀንዳውም ሊቃውንት ጉባኤው “የሐይማኖት ህጸጽ” አለባቸው ተብለው ስለ ቀረቡ ወገኖች አጣርቶ የደረሰበትን እንዲያቀርብ ማድረግና ውሳኔ መስጠት ነበር። በዚህም መሰረት ማቅ ይወገዙ ይከሰሱልኝ ሲል ካቀረባቸው ሰዎች መካከል የአባ ሠረቀ ብርሃን እና የዲ/ን በጋሻው ጉዳይ ታይቶ ነፃ መሆናቸው ተረጋግጧል። ይህ ውሳኔ ለማኅበረ ቅዱሳን ትልቅ ውድቀት እንደሆነ ታዛቢዎች እየተናገሩ ይገኛሉ። 
አባ ሰረቀ በነበሩበት የሰንበት ማደራጃ መምሪያ ኃላፊነት ሕግን ማስከበር ግዴታቸው ስለሆነ ማኅበሩ በመተዳደሪያ ደንቡ መሰረት ሊያሟላ የሚገባቸውንን መስፈርቶች አሟልቶ ሊፈጽም የሚገባቸውን ግዴታዎች ፈጽሞ በሕጋዊነት ይንቀሳቀስ ማለታቸው “የኑፋቄ መጨረሻ” ነው ብሎ ከፍተኛ ፕሮፓጋንዳ በተለያየ መንገድ ሲዘራባቸው የነበረው ማኅበረ ቅዱሳን በቅዱስ ሲኖዶሱ ውሳኔ አንገት ደፍቷል። ከጥቅምቱ ሲኖዶስ ስብሰባ በኋላ የአባ ሰረቀ ክኅነት እንደተያዘ በማስመሰል አባላቱ አምደኞች በሆኑባቸው እና ድርጎ ቀማሽ በሆኑ ጋዜጦችና በብሎጎቹ ከፍተኛ የስም ማጥፋት ዘመቻ አድርጎ የነበረ ቢሆንም ሊቃውንት ጉባኤው በተሻለ ጥንቃቄ ነገሮችን ተመልክቶ የሚወራባቸው ወሬ ሁሉ ፍሬ ከርስኪ መሆኑን አሳይቷል። ይህ ውሳኔ ለአባ ሠረቀ ብርሃን ትልቅ ድል መሆኑም የሚታይ እውነት ነው።
ማኅበረ ቅዱሳን ዲ/ን በጋሻውንን ከሚቃወምበትና መናፍቅ እያለ ስሙን ማጥፋት የጀመረበት ምክንያቶች ሦስት ሲሆኑ እነርሱም ከአቡነ ጳውሎስ ጋር መታረቁ፣ ማኅበሩን በስህተቶቹ አደባባይ ላይ መውቀሱ እና በካሴት ሽያጭ ደግሞ የአንበሳውን ድርሻ ወውሰዱ ናቸው።

ከአቡነ ጳውሎስ ጋር በታረቀ ጊዜ “ገዝግዘን ገዝግዘን ልንጥላቸው በነበረ ጊዜ ከእሳቸው ጋር ታርቆ በርካታ ቁጥር ያላቸው ደጋፊዎቹን ለእሳቸው ያለው አስተያየት ወደ መልካም እንዲለወጥ አድርጓል። ይህም ለፓትርያርኩ ተጨማሪ ጥንካሬን ሰጥቷል። በማለት ገና የማጥላላት ዘመቻውን ከመጀመራቸው በፊት በንዴት ሲናገሩ የተሰሙት አንዳንድ የአመራር አባሎች ይህ ንግግራቸው በወቅቱ በቅርብ በሚያውቁዋቸው ሰዎች ዘንድ ለከፍተኛ ትዝብት ዳርጓቸው እንደነበር አይዘነጋም።
 ከዚህም ጋር ተያይዞ ማቅ ችግር በሚፈጥርባቸው ነገሮች ላይ መናገር መጀመሩ በማህበሩ በተሃድሶነት ለመወገዝ ተጨማሪ ምክንያት ሆኗል። ዲያቆን ዳንኤል ክብረት እንዳለው ደግሞ በጋሻው ማኅበሩን መንቀፉ “ተሀድሶ” ተብሎ የተነከሰበት ጥርስ እንዲጠብቅ ተጨማሪ ምክንያት ሆኗል። ዲ/ን ዳንኤል ባለፈው አመት በለቀቀው ጽሁፉ ስለ ዲ/ን በጋሻው እንዲህ ብሎ ነበር “ዲያቆን በጋሻው ማስተማር የጀመረው መቼ ነው? ማኅበሩ በነዲያቆን በጋሻው ላይ ሃሳብ ዛሬ መሠንዘር ለምን ጀመረ? በጋሻው ለቤተ ክርስቲያን አደጋ ነው ብሎ ስላሰበ አይደለም። በጋሻው ማኅበረ ቅዱሳንን በተመለከተ ስለ ተናገረ ነው። ከዚህ በፊት ምንም ያልተናገረው ማኅበር ስሙ ሲነሳ ቤተክርስቲያን ተነካች ብሎ ተነሣ።” ይህ የዳንኤል ውስጥ አወቅ ጽሁፍ ማኅበሩ እንዴት ባለ ውድቀት ውስጥ እንዳለ እና እኔን የተቃመወና ስህተቴን የነገረኝ ሁሉ የቤተክርስቲያን ጠላት ተሃድሶ መናፍቅ ነው በሚል አባዜ እንደሚመራ ያሳየ እና የበጋሻው ችግር ሃይማኖታዊ አለመሆኑን ያሳወቀ ነበር። (በነገራችን ላይ ዲ/ን ዳንኤል ከማኅበሩ ጋር የገባው ውዝግብ በይቅርታ ሳይፈታ አንድ ሳምንት እንኳ ቢዘገይ ኖሮ በዘሪሁን ሙላቱ አማካኝነት ዕንቁ መጽሔት ላይ እንዲወጣ የተዘጋጀ ጽሁፍ ነበር። እርቁ የዘሪሁን ተሳዳቢ ብዕር ያጠቆረውን ወረቀት ማረፊያ አሳጥቶታል።)
 ከዚህ ጋር ተያይዞ ሦስተኛው ምክንያት ደግሞ የዲ/ን በጋሻው የስብከት ሲዲዎች በከፍተኛ ቁጥር መሸጣቸው የማኅበሩን ሲዲዎች ከገበያ ውጭ በማድረጉ ማቅ በሚመራበት የቢዝነስ ሕግ ደግሞ “ተቀናቃኝህን እና ገበያ ላይ ፍርሀት የሆነብህን ሰው ማንኛውንም መንገድ ተጠቅመህ አስወግድ” የሚል በመሆኑ በጋሻውን ከገበያ ለማስወጣት  “ተሃድሶ መናፍቅ” የሚል ዘመቻውንን በተጠናከረ መንገድ ለመጀመር አስችሎታል። 
ማቅ በተለያየ መንገድ ሊያጠፋ ሚፈልገውን ሰው ሁሉ ህዝቡን በቀላሉ ለማሳመን በሚረዳው “ታድሰዋል  መንፍቀዋል” በሚል መንገድ ከሶ ስለሚያጠቃ ምንም እንኳ አባ ሠረቀ እና ዲ/ን በጋሻው ከእነርሱ ጋር ያልተግባቡበት መንገድ የተለያየ ቢሆንም የከሰሱዋቸው ግን በአንድ ስም “ተሀድሶ መናፍቅ” ብለው ነው።
የቅዱስ ሲኖዶሱ ውሳኔ ማኅበረ ቅዱሳን አካሄዱን እንዲፈትሽና እኔን ያልተቀበለ ሁሉ መናፍቅ ነው ከሚያሰኝ አባዜው በቶሎ ሳይመሽበት ነጻ እንዲወጣ አቅጣጫ ጠቋሚ መሆኑም ተመልክቷል። 
 http://www.abaselama.org/2012/05/blog-post_11.html

Clergy of the European Diocese convened in Geneva .

Clergy of the European Diocese convened in Geneva .  

To assess the needs of the Eritrean faithful in the European countries, Clergy of the European Diocese of the Eritrean Orthodox Church convened in Geneva, Switzerland.
The three-day meeting took place on May 4–6, 2012.
To meet the spiritual needs of the church’s faithful, the clergy elected seven people that consist of five clergies.  Under the guidance of His Grace Bishop Mekarios, the elected servants will serve the Diocese in the following dimensions:
Fr. Tekle-mariam, chair
Fr. Yonas, secretary
Fr. Phanuel, education
Fr. Mulu-Berhan, public relations
Fr. Habtom, communication
Mr. Daniel Kesete, finance and accounting
Mr. Berhane Hadege, document control

Representing His Grace Bishop Mekarios, Fr. G. Michael Yohannes, priest of Medhane-Alem Church of Atlanta, GA, USA, participated at the clergy meeting. On his return, Fr. Yohannes will report directly to His Grace on the Diocese’s successful meeting.
It is to be remembered that the European Diocese was established in December 2011 by His Grace Bishop Mekarios, Bishop of the North American Archdiocese of the Eritrean Orthodox Church.
May God bless Eritrea and its people.
            haymanoteabow@gmail.com
 

ኣታ ሰማይ ብኣኣ ተሓጎስ ኣቱም ቅዱሳትን ሃወርያትን ነበያትን ኣምላኽ ኣብኣ ፍርድኹም ተፈድዩ እዩ እሞ ፡ብኣኣ ተሓጎሱ ራእ18፡20።

ኣታ ሰማይ ብኣኣ ተሓጎስ  ኣቱም ቅዱሳትን ሃወርያትን ነበያትን  ኣምላኽ ኣብኣ ፍርድኹም ተፈድዩ እዩ እሞ ፡ብኣኣ ተሓጎሱ ራእ18፡20።
ሃገረ ስብከት ኣውረጳ ጉባኤኡ ኣካይዱ  ካህናት ባዕሎም ብ ባዕሎም ብዘይ ዝኾነ ፖሎቲካውን ደጋውን ተጽዕኖ ዉሉደ ክህነትን ኣመንትን ተሳተፉዎ ትስፉው ዝኾነ ጉባኤ ብሓቂ ተኣምራታዊ ዝኾነ ጉባኤ እዩ ነይሩ።ኣብ ታሪኽ ቤተ ክርስትያን ናይ ኤረትራ  ኩሉ ዝግበር ነብረ እንበኣር  ተጽዕኖ ናይ ኤረትራ ፖሎቲከኛታት ዝነበሮን ን ዝረብሓ ቤተ ክርስትያን ዘይውክልን እዩ ነይሩ።ሎሚ ግን ታሪኽ ተሰሪሑ ኣብ ጉባኤ ጀነቫ ድምጺ ኣገልገልቲ ኣምላኽ ብዓውታ ተቃሊሑ።
ኣብ ሓንጎል ብዙሓት ሰባት ናይ ተዋህዶ መራሕቲ ባዕሎም ንባዕሎም ክመዓዓዱን ዘሎ ሽግር ክፈትሑን ኣይክእሉን እዮም ኢልካ ዝንዛሕን ዝውረን ነበረ  ሎሚ መልሲ ረኺቡ።ብሓቂ ቤተ ክርስትያን ህላወኣ ዘረጋገጸ ዕለት ፡ወንጌል ከም ዘይሰዓር ዘርኣየት ወርቃዊት ዕለት፡ብሓቂ ነዚ መዓልቲ ዕለት እዚ ክዝክር ከለኹ ብሂል ናይ ሓደ ኣቦ ዘኪረ ፡<<ጅግና ተኸደ ጅግና ነይነዲ >>ተባሂሉ። እወ ሎሚ እንበኣር ተዋህዶ ዋላኳ ናይ እምነት ጀጋኑ ብዙሕ ግዜ ተጠፍአት ፡ግን  እዚ ንሪኦ ዘለና ጩራስ ነቲ ዝደመየ ልቢ ቤተ ክርስትያን ዝድብስ ይመስል ።ሎሚ ኣታ ሰማይ ብኣኣ ተሓጎስ ክንብል እንደፍረላ መዓልቲ  በጺሕና!!!።
ናይ ሃወርያትን ነበያትን ጻድቃንን ፍርዲ ዝተተግበራላ መዓልቲ። ኣቱም ቅዱሳትን ሃወርያትን ነበያትን  ኣምላኽ ኣብኣ ፍርድኹም ተፈድዩ እዩ እሞ ፡ብኣኣ ተሓጎሱ ራእ18፡20። ቅዱሳን ዝተሓጎሱላ መዓልቲ እወ እቲ ኣብ (ቀኖና ጋንግራ 325-381ዓ.ም. ቀኖና 3)።ፍትሕ መንፈሳዊ ዓንቀጽ 5፡ 172- 185 ዘውጽእዎ ሕጊ ዝተተግበረላ መዓልቲ  ቃሎም ዝኸበረላ መዓልቲ። ቀኖናን ስርዓትን ቅዱሳን ብ ጉባኤኦም ኣጽዲቆሞ ዝኸዱ ኣብ ግብሪ ዝወዓለላ መዓልቲ፡ሕድሮም ተተግቢሩ ዝቀሰኑላ መዓልቲ፡ማቴዎስ 22፡21 ።ናይ ቀሳር ንቀሳር ናይ ኣምላኽ ን ኣምላኽ ዝተባህለላ መዓልቲ እቶም ደቂ ኣምላኽ ኢህን ሚህን ዝተባህሉላ መዓልቲ ከም ምኻና መጠን ነቶም ነዚ ወንጌል እዝን ነዚ ስርዓትን ቀኖናን ቤተ ክርስትያን  እዝን ኣብ ኢድና ክበጽሕ ዝገበሩ ስለ ክርስቶስ ሂወቶም ዝሃቡ ቅዱሳን በዛ መዓልቲ እዚኣ ተሓጎሱ ንብሎም።ከመይ ከ ዘይሕጎሱ ቃሎም ተትግቢሩ፡ ።ኣምላኽ ኣብ ማእከልና ተኣምራት ገይሩ።
እወ እግዚኣብሄር ይመስገን ን ብዙሓት ዓለወኛታት ዘፍዘዘት መዓልቲ፡ ኣብ ኣስመራ ኮነ ኣብ ካልእ ከባቢታት ተፋላለዩ ዓመጸኛታት ስንባደን ነውጽን ምዕልባጥን ከም ዝፈጠረሎም ኣቦው ካብ ዝመጹዎ መልእኽታት ተረዲኡ ኣሎ።ማቴዎስ 23፡23-36 እቶም ግቡዛት ቃርማ መጺጹዎም ጡፍ ዝብሉ  ገመል ግን ዝውሕጡ ዕዉራት መራሕቲ ዝብልዎ  ብፍላይ ድማ እቶም ኣብ ኣስመራ ን ሓቂ ንምዕባጥ ግዝይኦም ዘጥፍኡ ዘለዉ ። ንሓቂ ኣብ ዘይፍለጥ ጸልማት ዓቢጦም ክነብሩ ዝመሰሎም  ኣብ ኣውረጳ በዚሓስን ሰዊዳን ኣይፋል ሓሶት ያኣክል ህጅስ ክትብል ከላ፡ ሓቆም እዮም ዘየሰንብድ ኣይኮነን ፡ምእሳር ቅዱስ ፓትሪያርክን  ናይዞም ( 4 )ኣርባዕተ ኣቦታትን ሞነኮሳትን  ደኣሞ እንታይ ዋጋ ኣለዎ ተባሂሉ።እወ ከም ወዮ ቃል ኣምላኽ ካብ ነቢ ዝዓቢ ነቢ ኣብዚ ኣሎ ዝበሎ።ካብ ዶጓትር ዝበልጹ ዶጓትር፡ካብ ሊቃውንቲ ዝበልጹ ሊቃውንቲ ስለ ክብሮም ዘይኮነስ ስለ ቤቱን ወንጌሉን ከይደቀሱ ዝሓድሩ መንእሰያት ግን ከ ናይ ዓበይቲ ኣተሓሳስባ ዘለዎም፡ከም ወዮ ቃል ኣምላኽ ዝበሎ  ሎሚ ዝኾነ ስንባደ ተመጸ ኣይገርመናን እዩ።
ስለምንታይ ታሪኽ ክድገም  ባህርያዊ እዩ።ማቴዎስ 2፡3ንጉስ ሄሮዶስ ሰሚዑ ሰንበደ ኩላ ኢየሩሳሌምውን ምስኡ። ክርስቶስ ብምውላዱ ዝሰንበዱ ከተማታትን ሕልቅነት ስልጣናትን ሎሚ እቶም ንክርስቶስ ዝውክሉ ክንዲ ክርስቶስ ኮይኖም ምስ ክርስቶስ ተዓረቁ ዝብሉ ሉኡኻት ወንጌል ክርስቶስ ክእከቡ ከለዉ፡ ከመይ ዲያብሎስ ዘይስንብድ እዚ ጉባኤ እዚ ምፍራስ ያርኮ ዘመልክት እዩ።ህጂ ዘድልየና ሓደ ክልተ ሰለስተ ኣርባዕተ ኢልካ ምፍቃድ ጥራሕ እዩ ቀጽሪ ያሪኮ ክፈርስ።2ይ ቆሮንቶስ5፡20-21። ሰጣን ኣዋጅ ኲናት ኣብ ልዕሊ ሕልቅነት መናፍስቲ ስለ ዝኾነ ብዘሎ ንሱ ሒዝዎም ዘለዉ ክስንብዱ ግድን እዩ።
እዞም ካብ ተፋላለያ ሃገራት ኣውረጳ ነን ቤተ ክርስትያናቶም ወኪሎም ዝመጹ ዉሉደ ክህነት ኣብ ገጾም ዝንበብ ነበረ  ሓላፍነታውነት ናይታ ደቃ መዓልታዊ ትኸስር ዘላ ቤተ ክርስትያን እዩ። ብሓቂ ድማ ከመይ ገይሮም ነቲ ፈቀዱኡ ሰኣን ሓቀኛ ጓሳ ወንጌል ፋሕ ኢሉ ዘሎ ሞጓሰ ከመይ ገሮም ይእክቡዎ ብ ሓንጎል ተረዳድኡ እዮም ምዃኖም ኣብ ገጾም ይንበብ ነሩ። እቲ ናይ ጸጋም ኢድ የእታውነት ኣብ መንጎ መራሕቲ ኦርቶደክስ ዝግበር ነበረ ናይ ዘይ ምትእምማን መንፈስ ንምፍጣር ሰጣን ዝጥቀመሉ ሜላ እውን ድሮ ተረዲኦሞ እዮም ።ድንዕኦም ሎሚ ሽርሕን ጉርሕን ጸላእቲ ወንጌል ከም ድሙቅ ብርሃን በሪሁሎም እዩ።።ጉባኤኛታት ን ቤተ ክርስትያኖም ሓፍ ንምባል ካብ ዝኾነ ፖሎቲካዊ ኣታሓሳስባቶም ወጺኦም እቲ ኣብ ክርስቶስ ዝነበረ ኣተሓሳስባ ኣባኻትኩም። ይሃሉ ዝብል ኣብ ግብሪ ዘውዓሉላ እያ ነይራ።ሎሚ ን ኣምላኽ  ከነመስግኖ ይግብኣና  ከምዚኦም ዝበሉ ኣቦታት ስለ ዝሃበና፡እንተ ሳንባላጥ ግን ነህምያ 2፡19ኣምላኽ ተዛሪቡ ንብሎ።
             እግዚኣብሄር ሃይማኖትና ይባርኽ
             ንቅዱሳን ኣቦታት እውን ኣብ ኣገልጊሎቶም ኣሳልጦ ንምነ።
                 ስብሃት ለእግዚኣብሄር